የአቪዬሽን ስትራቴጂካዊ አጋርነት እና የአፍሪካውያን የተቀላጠፈ እንቅስቃሴ

June 16
1 hr

View Transcript

Episode Description

''አሁን ላይ የባህረ ሰላጤው አየር መንገዶች ወደ አህጉራችን የሚያደርጉት መስፋፋት ለአፍሪካ አየር መንገዶች ስጋት ሳይሆን፣ አህጉራዊ ትስስራችንን የሚያጠናክር እና ከዓለም አቀፉ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ አዲስ የትብብር ኮሪደር የሚከፍት ትልቅ ዕድል ነው። ዋናው ቁምነገር ብሔራዊ አየር መንገዶቻችን ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም የራሳቸውን የንግድ አቅምና መዋቅር በማሳደግ፣ የጋራ የአፍሪካ ነፃ የአየር ትራንስፖርት ገበያን በተግባር ለማገዝ ስልታዊ በሆነ መንገድ እንዴት መተባበር እንዳለባቸው ማወቃቸው ላይ ነው'' ሲሉ የአቪዬሽን ዘርፍ ስትራቴጂስት እና አማካሪ ሾን ሜንዲዝ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።

በዛሬው የተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፖድካስታችን በቀዳሚነት የአቪዬሽን ትስስርን በተመለከተ የኢትሃድ አየር መንገድ ወደ አፍሪካ የሚያደርገው መስፋፋት እና የደቡብ ለደቡብ የንግድ ትስስርን ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከአቪዬሽን ዘርፍ ስትራቴጂስት እና አማካሪ ሾን ሜንዲዝ ጋር እንወያያለን። የዲጂታል ጉዞ ፈቃድ (ETA) የአፍሪካውያንን ነፃ እንቅስቃሴ ማቀላጠፍ እና የኢኮኖሚ ህዳሴን ስለማምጣት ከቱሪዝም መዳረሻዎች አማካሪ አንቶኒ ኦቺዬንግ ጋር በጥልቀት እንነጋገራለን።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ይከታተሉ ፦


See all episodes