የቶጎ ታሪካዊ የቪዛ ስረዛ ከአፍሪካውያን የጋራ እጣ ፈንታ አንጻር

July 18
1 hr

View Transcript

Episode Description

''አፍሪካውያን በገዛ አህጉራቸው በነፃነት እንዲንቀሳቀሱ እና ሀብታቸውን፣ እውቀታቸውንና አቅማቸውን እንዲያስተሳስሩ መፍቀድ የቅንጦት ጉዳይ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው ። ቶጎ የወሰደችው የድንበር መክፈት ውሳኔ፣ አህጉራዊ ትብብርን ከተራ የፖለቲካ መግለጫዎች ባለፈ በተግባር ማረጋገጥ እንደሚቻል ያሳየ ደማቅ የአንድነት ማሳያ ነው'' ሲሉ የዘላቂ ቱሪዝም ተንታኝ ጁዲ ኬፐር-ጎና ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል ። 

በዛሬው የተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፖድካስታችን፤ የምዕራባውያንን ተጽዕኖ እና የቅኝ ግዛት የድንበር ከፋፋይ አጥርን በተግባር ስለሰበረው የቶጎ ታሪካዊ የቪዛ ነፃ ፖሊሲ በሰፊው እንወያያለን ። ፕሮግራማችን ትኩረቱን የሚያደርገው የአፍሪካ ሀገራት በጋራ በመቆም የራሳቸውን መዋቅራዊ ሉዓላዊነት እንዴት ማጠናከር ይችላሉ በሚለው ላይ ነው ። 

ጠንካራ የአፍሪካ-ለአፍሪካ የጉዞ እና የንግድ ትስስር መፍጠር ስለሚቻልበት ሁኔታ ፣ አህጉራዊ ካፒታል ወደ ውጭ ሀገራት የኦንላይን ፕላትፎርሞች እንዳይፈስ ለመግታት ወጣት የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችን በጋራ ስለማብቃት ፣ እንዲሁም የኢኮኖሚ ስኬታችንን በምዕራባውያን መለኪያ ሳይሆን በአፍሪካውያን ማህበረሰቦች የጋራ ተጠቃሚነት እና ሁለንተናዊ ደህንነት ለመለካት በሚያስችሉ አዳዲስ መዋቅሮች ዙሪያ ከኬንያዊቷ የቱሪዝም ባለሙያ ጁዲ ኬፐር-ጎና ጋር በጥልቀት ተወያይተናል ። 

ሙሉውን መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

See all episodes