Episode Description
"ከቅኝ ግዛት ዘመን ጀምሮ የአፍሪካ ኢኮኖሚ መዋቅር ለምዕራባውያን ተገዢ እንዲሆን ተደርጎ ነው የተቀረጸው። የአሁኑ የዓለም አቀፍ አቅርቦት ሰንሰለት መቋረጥ ግን ወደ ውስጥ እንድንመለከት፣ አምራች እንድንሆን እና በአህጉራዊ የነፃ ንግድ ቀጠና በኩል እርስ በርስ እንድንተሳሰር ትልቅ ዕድል የፈጠረልን 'የመቀስቀሻ ደወል' ነው።" ሲሉ በኢትዮጵያ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ ጀማል መሐመድ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት በክፍል አንድ፦ የአፍሪካ የንግድ ሪፖርት 2026ን መነሻ በማድረግ የዓለም ፖለቲካዊ መዋዠቅ ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ሽግግርና ለአህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጠና ምን ዓይነት አዳዲስ ዕድሎችን ይዞ መጥቷል? ስንል ከከፍተኛ ተመራማሪው ጀማል መሐመድ (ዶ/ር) ጋር ያደረግነውን ጥልቅ ውይይት ይዘንላችሁ ቀርበናል። በክፍል ሁለት፦ የአፍሪካ በጎ አድራጎት ለምን የአህጉሪቱን እውነታ ማንጸባረቅ ተሳነው? በባህላዊ እውነታዎች ላይ ተመስርቶ እንዴት በድጋሚ ሊዋቀር ይችላል? ስንል የሲቪ (SIVI) ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ቴንዳይ ሙሪሳ እና የጋልቫናይዚንግ አፍሪካ ኮንሰልት የልማት አማካሪ ጃኔት ማዊዩ ሰፊ ማብራሪያ ይሰጡናል።
ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ: