የባህል ኃይል፦ ባሕላዊ አመራር፣ ፋሽን እና የአፍሪካ የወደፊት ጉዞ

February 4
1 hr

Episode Description

“የዓለም አቀፍ ሕግ፣ በምዕራባውያን ወገን ሕጎች የሚጥሱትን እንዲታሰሩ የሚያደርግ ነው። አንድ አፍሪካዊ መሪ በፖለቲካዊ መልኩ የአፍሪካን መንገድ ለመከተል ከወሰነ፣ ኢላማ ይደረጋል። በአንተ ላይ መጥፎ የሆኑ ስሞችን በመለጠፍ መገናኛ ብዙኃንን ተጠቅመው ሕዝቡ አንተን በመጥፎ ዓይን እንዲመለከትህ ማድረግ ይጀምራሉ። ይህንንም በአንተ ላይ የሚወስዱትን እርምጃ ትክክለኛ እንደሆነ ለማስመስል ይጠቀሙበታል። እስካሁንም ያለው አካሄድ ያው ነው።” ሲሉ በጋና ባሕላዊ መሪ እና የ‘ዘ ቴስት ኦፍ አፍሪካ’ ተባባሪ መስራች የሆኑት ቴንጎል ኬፕሌማኒ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል፣ በጋና ባሕላዊ መሪ እና የ‘ዘ ቴስት ኦፍ አፍሪካ’ ተባባሪ መስራች እና የ‘ካልቸራል ዋንነስ ፌስቲቫል’ አዘጋጅ ቴንጎል ኬፕሌማኒ ጋር በመሆን — በፍጥነት እየተለወጠ ባለው ዓለም ውስጥ የአፍሪካ ወጎች እንዴት አግባብነታቸውን ጠብቀው ሊቀጥሉ እንደሚችሉ እንወያያለን። በሁለተኛው ክፍል ደግሞ የ‘አፍሪካ ሞዛይክ’ የፋሽን መድረክን አስታከን ከቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ እና ከታዋቂው ሙዚቀኛና አርቲስት ስለሺ ደምሴ (ጋሼ አበራ ሞላ) ጋር ስለ ባህል ዲፕሎማሲ እና ተያያዥ ጉዳዮች ያደረግነውን ቆይታ አካትተናል።

ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

See all episodes