ከአእምሮ ነፃነት እስከ አህጉራዊ የውኃ ሀብት ሉዓላዊነት

July 11
1 hr

Episode Description

 "የአፍሪካ ትራንስፎርሜሽን ጉዞ የእውቀት ምርትን፣ ታሪካዊ ትውስታን እና ምሁራዊ ነፃነትን መልሶ ከመያዝ ትግል ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነው። የትምህርት ሥርዓቶቻችን እና የታሪክ ትረካዎቻችን ከአሮጌው የቅኝ ግዛት አስተሳሰብ ነፃ ካልወጡ አህጉሪቱ እውነተኛ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ አትችልም።" ሲሉ የፓን-አፍሪካን አስተሳሰብ ትምህርት ቤት መስራች እና ዳይሬክተር ናይጄል ስቴዋርት ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡   

በዚህኛው ባለሁለት ክፍል የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን፣ «አእምሮን ከቅኝ ግዛት አስተሳሰብ ማውጣት፦ ትምህርት፣ ታሪክ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ መጻኢ ዕድል» በሚለው ዋና አጀንዳ ላይ ከፓን-አፍሪካን አስተሳሰብ ትምህርት ቤት መስራች እና ዳይሬክተር ከናይጄል ስቴዋርት ጋር ሰፊ ውይይት ያደረግን ሲሆን፤ የትምህርት ሥርዓቶች ንቃተ-ህሊናን እንደሚቀርጹ ሁሉ የልማት ሥርዓቶችም ነባራዊ እውነታን ይወስናሉ በሚለው መርህ፣ በሁለተኛው የዝግጅታችን ክፍል ደግሞ የአፍሪካ የጋራ የውኃ ሀብቶች በጂኦፖለቲካዊ ክፍፍል ምትክ እንዴት የአህጉራዊ ውህደት እና የብልጽግና መሣሪያ መሆን እንደሚችሉ በውኃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከፍተኛ አማካሪ ከሆኑት ከኢንጂነር ተፈራ በየነ ጋር በዝርዝር ተወያይተንበታል።

ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:


See all episodes