ሉዓላዊነት በተግባር፡ ከዓለም አቀፍ አጋርነት እስከ አፍሪካ የጤና ነፃነት

June 23
1 hr

Episode Description

“ከብሪክስ  አንጻር ሲታይ፣ ኢትዮጵያንና ጥቂት ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትን ያካተተ ዘርፈ-ብዙ ገጽታ አለው። ይህ ዘርፈ-ብዙ ግንኙነት ራሱ የአፍሪካ-ሩሲያን ግንኙነት ለማጠናከር የበኩሉን አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን፣ ይህም የደቡብ-ደቡብ ትብብር  ዋነኛ ምሰሶ ነው። እንዲሁም ይህ ግንኙነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣ ነው። ይህ ግንኙነት እየሰፋ የመጣ መስክ ያለው ሲሆን፣ ለሁለቱም ወገኖች ማለትም ለሩሲያ ፌዴሬሽን እና ለአፍሪካ ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ነው።” ሲሉ በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የውጭ ግንኙነትና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ 

በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት በፍጥነት እየተለዋወጠ ባለው የዓለም ሥርዓት ውስጥ የአፍሪካን ድርሻ የሚዳስስ ጠንካራ የሁለት ክፍል ውይይት ይዘንላችሁ ቀርበናል። በክፍል አንድ የፖለቲካ፣ የደህንነት፣ የኢኮኖሚ እና የሰብዓዊ ግንኙነቶችን ትብብር የሚቀርፀውን የሩሲያ–አፍሪካ አጋርነት መድረክ የድርጊት መርሃ ግብር (2023–2026) ከአምባሳደር ዲና ሙፍቲ ጋር እንመረምራለን። 

በክፍል ሁለት፡ በአዲስ አበባ (መጋቢት 18–19 ቀን 2018 ዓ.ም) በተካሄደው 62ኛው የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር አመታዊ ጉባኤ ላይ በመገኘት፣ የአፍሪካን የጤና ስርዓት ከጥገኝነት ለማላቀቅና ራስን ለመቻል የሚደረገውን አስቸኳይ ጥረት ከፕሮፌሰር ጆን ዌሩ፣ የክሊኒካዊ ጉዳዮች ባለሙያ፣ ከዶ/ር ሙባረክ ሸምሱ፣ የህብረተሰብ ጤና ስፔሻሊስት እንዲሁም ከቤተልሄም በቃሉ፣ የ5ኛ ዓመት የህክምና ተማሪ ጋር እንቃኛለን። 

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ 

See all episodes