81ኛ ዓመት የድል ቀን መታሰቢያ፦ የኢትዮጵያና የሶቪየት ህብረት የጋራ የፀረ-ፋሺዝም ትግል

June 3
1 hr

Episode Description

"የሶቪየት ህብረት በናዚ ጀርመን ላይ የተቀዳጀችው ድል የሩሲያውያን ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያውያንም ጭምር ነው፤ ምክንያቱም ሁለቱም ሀገራት ለነፃነትና ለሉዓላዊነት ሲሉ ለከፈሉት መስዋዕትነት ትልቅ ማሳያ በመሆኑ ነው።" ሲሉ የታሪክ ተመራማሪውና ደራሲ አቶ ጥላሁን ጣሰው ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡

"በናዚ ጀርመን ላይ የተገኘው ድል የሁላችንም ድል ነው፤ ለሩሲያውያን ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካውያን በተለይም ደግሞ ላልተገዛችው ኢትዮጵያ ትልቅ ትርጉም አለው፡፡" በማለት ፕሮፌሰር ዳንኤል ቅጣው አክለዋል፡፡

በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ መሰናዶአችን፤ የሶቪየት ህብረት በናዚ ጀርመን ላይ ድል የተቀዳጀችበትን 81ኛ ዓመት መታሰቢያ አስመልክቶ፣ በኢትዮጵያና በሩሲያ መካከል ያለውን የታሪክ ቁርኝት እንቃኛለን። በውይይታችንም የታሪክ ተመራማሪውና ደራሲ አቶ ጥላሁን ጣሰው እንዲሁም የአርበኛው ፊታውራሪ ቅጣው አዘነ ልጅ እና እና ታሪክ ወዳዱን የኢንዱስትሪ ኢንጂነሪንግ ፕሮፌሰር ዳንኤል ቅጣው እንግዶቻችን አድረገናቸዋል።


See all episodes