ከሆርሙዝ እስከ ብሪክስ፡ የኢራን ውጥረት የዓለምን የኃይል የበላይነት እንዴት እየቀየረው ነው?

August 20
1 hr

Episode Description

«አሜሪካ በኢራን ላይ በርካታ ሙከራዎችን አድርጋለች፣ ነገር ግን የኢራንን ኃይል መቆጣጠር አልቻለችም... ጦርነቱ እየሰፋ ከሄደ እና ኢኮኖሚው ጥያቄ ውስጥ ከገባ፣ አሜሪካ አሁን እውነተኛ ተፅዕኖ ላላቸው ብሪክስን ጨምሮ ለተቀናጁ ሀገራት እጇን ለመስጠት ልትገደድ ትችላለች።» ሲሉ በወራቤ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ረዳት ፕሮፌሰር መሐመድ ኢሳ ሹራላ (ዶ/ር) ስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ 

በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ በሆርሙዝ ሰርጥ ያለው የጂኦፖለቲካ ውጥረት በአፍሪካ የኢነርጂ ደህንነትና ኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድረውን ተፅዕኖ እንቃኛለን። በሁለተኛው ክፍላችን ደግሞ፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የሚፈጥረውን ዕድል ወደ ተጨባጭ ንግድ ለመቀየር የሚያስፈልጉትን የሎጂስቲክስና የንግድ ትስስሮች ከመሳይ አየለ(ዶ/ር) ፣ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሎጂስቲክስና የአቅርቦት ሰንሰለት አስተዳደር ረዳት ፕሮፌሰር ጋር እንዳስሳለን።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ።


See all episodes