Episode Description
ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር በምዕራባውያን ላይ ያነሱት የሉዓላዊነት ጥያቄ የዓለምን ጂኦ-ፖለቲካ ቀይሮታል። ለዘመናት "ፀረ-ሽብር" በሚል ሽፋን የተካሄደው የሀብት ዘረፋ እና ጣልቃ ገብነት ሲያበቃ፣ ሀገራቱ ፊታቸውን ወደ ሞስኮ አዙረዋል። ለመሆኑ ይህ የሽግግር ወቅት ለአፍሪካ ኢኮኖሚያዊ ነጻነት እና ለባለብዙ ዋልታ የዓለም ስርዓት ምን ትርጉም አለው?
" የሩሲያና የአፍሪካ ግንኙነት የሚወሰነው በሩሲያና በአፍሪካ መሪዎች ነው። እና ይህ መሰረታዊ ነገር ነው። የሁለቱ ማለትም ሩሲያ እንደ አንድ ሀገር፣ አፍሪካ እንደ ብዙ ሀገር—የሚሰጡት፣ መሪዎቻቸው የሚወስኑት ነገር ወደፊት የሁለቱን ግንኙነት... የሚወስን ይመስለኛል።" — ፕሮፌሰር ዘነበ ክንፉ፣ በሩሲያ የኢትዮጵያውያን ማህበር ፕሬዝዳንት እና በሩሲያ የስቴት ዱማ የአፍሪካ ጉዳዮች ምክር ቤት ከፍተኛ አማካሪ
በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ የሳህል ሀገራት ኮንፌዴሬሽን (AES) ምስረታን፣ የሩሲያን የ"ያለ ጣልቃ-ገብነት" የአጋርነት መርህ እና የአፍሪካን አዲሱን የነጻነት ትግል ከፕሮፌሰር ዘነበ ክንፉ ጋር በሰፊው እንወያያለን።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡